የፋይናንስ እውቀትን ማጎልበትና የደንበኞችን ጥበቃ ማጠናከር

ከጥቅምት 17 – 21፣ 2018 ፡ አገር አቀፍ ዘመቻ – መክፈቻ መርሐግብር በጋምቤላ ክልል በጋምቤላ ከተማ

አገር አቀፍ ዘመቻ

ዓመታዊው የፋይናንስ ዕውቀት ሳምንት 2018

የ 2018  አገር አቀፉ ዓመታዊው የፋይናንስ ትምህርት ሳምንት ዘመቻ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተዘጋጀ ሲሆን በተባባሪነት በፋይናንስ ዘርፍ የሴቶች ጥምረት (NEWFin)፣ የተባበሩት መንግስታት ካፒታል ልማት ፈንድ(UNCDF) ሰዊፍት(SWIFT) ፕሮግራም የክልል መንግስታትና የፋይናንስ ተቋማት ይሳተፋሉ፡፡ መሪ ቃሉ “የፋይናንስ ትምህርትን ማጎልበትና የደንበኞችን ጥበቃን ማጠናከር” ሲሆን ዋና ዓላማውም አገር አቀፉን የፋይናንስ ትምህርት ስትራቴጂ መሠረት በማድረግ የወጣቶችን የፋይናንስ ደህንነት ማሳደግና በአገር አቀፍ ደረጃ የፋይናንስ ተደራሽትን ማስፋት ነው፡፡

የዚህ ዓመቱ ዘመቻ በዋናነት ትኩረት ያደረገው የሞባይል ገንዘብ ትምህርትና የደንበኞች ጥበቃ ላይ ሲሆን በዚህም ወደ 3 ሚሊዮን የሚደርሱ ወጣቶችን ከነሱም ውስጥ ግማሽ የሚሆኑ ሴቶችን ማእከል አድርጓል፡፡ ለመድረስ የታቀደውም በማህበረሰብ አቀፍ ወርክሾፕ፣ በወጣቶች አቅም ግንባታ ፕሮግራም፣ የጎዳና ላይ ትዕይንቶች፣ በመገናኛ ብዙሀን በሚተላለፉ መልዕክቶችንና በፋይናንስ ተቋማት በሚካሄዱ የሂሳብ ማስከፈት ዘመቻዎች ነው፡፡

የተለያዩ የህብረሰብ ክፍሎችን ተደራሽ በማድረግና የደንበኞች ጥበቃን በማሳደግ የ 2018 ዓመታዊው የፋይናንስ ትምህርት ሳምንት የፋይናንስ አካታችነትን በማጠናከርና የፋይናንስ ደንበኞችን ዕምነት በመገንባት እ.አ.አ በ 2030 ለመድረስ በታቀደው የፋይናንስ አካታችነት ግብ ላይ የበኩሉን ድርሻ ያበረክታል፡፡

የጋምቤላ ክልል ለምን?

የጋምቤላ ክልል ዋና ከተማ የሆነችው ጋምቤላ የፋይናንስ ዕውቀት ሳምንት መክፈቻ ፕሮግራም እንዲካሄድባት የተመረጠችው በዋናነት የገጠሩም ሆነ የከተማው ነዋሪ መገናኛ ማዕከል ሆነ ስለምታገለግል ነው፡፡ ከተማዋ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ብታስመዘግብም በርካታ የከተማዋና የአካባቢዋ ነዋሪዎች ላይ የፋይናንስ ዕውቀት ውስንነት፣ የፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽነት ላይ እንቅፋቶች እና በቂ የሆነ የፋይናንስ መረጃ አለማግኘት ይስተዋላል፡፡

የገጠሩን ማህበረሰብ የፋይናንስ ዕውቀት ማጎልበት የብሔራዊው ፋይናንስ ስትራቴጂ ዋና አካል ነው፡፡ ይህም ጋምቤላ ክልልን የፋይናንስ ግንዛቤ በመፍጠር፣ አካታችነትን በማጠናከርና የገጠሩን ማሕበረሰብ በመረጃ ላይ የተመሠረት ውሳኔ እንዲወስኑ በማስቻል ረገድ ዋነኛ መነሻ ያደርጋታል፡፡

ከጥቅምት 17 – 21፣ 2018 ፡ አገር አቀፍ ዘመቻ – መክፈቻ መርሃግብር በጋምቤላ ክልል

የትኩረት ማእከሎችና የሚጠበቁ ውጤቶች

በአገርአቀፍ ደረጃ የሞባይል ገንዘብ ግንዛቤና አጠቃቀም ማሳደግ

የሴቶችን የፋይናንስ ተደራሽነት ሂሳብ በማስከፈትና በሌሎች አገልግሎቶች ማስፋት

በደንበኞች ጥበቃ ህዝቡ በፋይናንስ ተቋማት ላይ ያለውን እምነት ማጠናከር

በባለድርሻ አካላት መካከል ትብብርን ማጎልበት

ግልጸኝነትንና በመረጃ ላይ የተመሠረቱ ውሳኔዎችን ማሳድግ

ሴቶችንና የፋይናንስ አገልግሎት በአግባቡ ያልተዳረሰባቸው ማህበረሰቦችን ማገዝ

የወጣቶችን ተሳትፎና ሥራ ፈጠራን መደገፍ

በትምህርት ቤቶች የፋይናንስ ትምህርትን ማጠናከር

የእለቱ መርሃግብር

ከጥቅምት 17 – 21፣ 2018 ፡ አገር አቀፍ ዘመቻ
መክፈቻ መርሐግብር በጋምቤላ ክልል

የመክፈቻ መርሐግብር

ጥቅምት 17, 2018 • በጋምቤላ ክልል በጋምቤላ ከተማ

ዓመታዊው የፋይናንስ ዕውቀት ሳምንት 2018 መክፈቻ መርሐግብር በጋምቤላ ክልል በጋምቤላ ከተማ

Financial Literacy to Rural Communities

Tue, Oct 28 • Nationwide

Financial literacy to rural communities and Female Employees’ Workshop

  • Mobile money safety
  • Know your rights
  • How to complain
Workshops Youth

Workshop on Consumer Protection

Wed, Oct 29 • Workshop

Workshop on Consumer Protection for Financial Institutions

  • On-site demos
  • Support desks
  • Account opening
Branches Accounts

Youth & Schools

Thu, Oct 30 • Schools

School club sessions, teacher briefs, and entrepreneurship linkages for students.

  • Clubs & quizzes
  • Teacher briefs
  • Entrepreneurship
Schools Clubs

Field Visits & Media Coverage

Fri, Oct 31 • Nationwide

Field Visits, Results Sharing and Media Coverage

  • Regional roadshows
  • Live radio/TV
  • Closing metrics
Roadshows Media

ዋናዋና ተግባራት

የፋይናንስ ደንበኞች ጥበቃ

የማህበረሰብ አቀፍ ተሳትፎ

የፋይናንስ ትምህርት ለገጠሩ ማህበረሰብ

የሴት የፋይናንስ ተቋማት ሠራተኞች ወርክሾፕ

የጎዳና ላይ ትእይንት ዘመቻ የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ላይ

ወጣቶች

አጋር ድርጅቶች

ተሳታፊ የፋይናንስ ተቋማት

ለተጨማሪ መረጃ

ዓመታዊው የፋይናንስ ደንበኞች ሳምንት አስተባባሪ ቡድን

Hadush Gebru

+251 978 790 028

Elias Salah

+251 938 600 661

Tsion Girma

+251 961 555 000