አገር አቀፍ ዘመቻ

ዓመታዊው የፋይናንስ ዕውቀት ሳምንት 2018

ዓመታዊው የፋይናንስ ዕውቀት ሳምንት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሚመራ አገር አቀፍ የግንዛቤ መፍጠሪያ ዘመቻ ነው፡፡ መሠረት ያደረገው ብሔራዊውን የፋይናንስ ትምህርት ስትራቴጂ ሲሆን ከፋይናንስ አካታችነት ስትራቴጂ 2 ጋርም የተዛመደ ነው፡፡ የዘመቻው እቅድም የፋይናንስ ግንዛቤን በማሻሻል፣ የደንበኞችን ጥበቃ በማጠናከርና የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን በማስፋፋት የዜጎችን የፋይናንስ ደህንነት ማሻሻል ነው፡፡ የ 2018 ዘመቻ በዋናነት ትኩረት ያደረገው ስለሞባይል ገንዘብ ማስተማርን ሲሆን ትኩረቱም ሴቶችን፣ ወጣቶችንና በአግባቡ የፋይናንስ አገልግሎት ያልተዳረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን በፋይናንስ ሥርዓቱ ተደራሽ ማድረግና እምነት እንዲኖራቸው መደገፍ ነው፡፡

የፋይናንስ ትምህርት ሳምንት በዋናነት የፋይናንስ ተቋማትን፣ የመንግስት አካላትንና የልማት ድርጅቶችን በጋራ በማገናኘት በአገር አቀፍ ደረጃ የተቀናጀ የፋይናንስ ትምህርት መልእክቶችን ያስተላልፋል፡፡ ከዚህም ባሻገር በጾታ የተከፋፈለ መረጃ በማጠናከር ዘመቻው አካታች የሆነ የሚላካ በአገር አቀፍ ደረጃ ቅድሚያ የሚሠጠው መሻሻልን ለማምጣት አልሟል፡፡ በዚህም ዘመቻው አገሪቱ በረጅም እቅድ የያዘችውን ጠንካራ፣ ለሁሉም ተደራሽና ፍትሀዊ የሆነ የፋይናንስ ሥርዓት የመገንባት ራዕይን ያግዛል፡፡

የጋምቤላ ክልል ለምን?

የጋምቤላ ክልል ዋና ከተማ የሆነችው ጋምቤላ የፋይናንስ ዕውቀት ሳምንት መክፈቻ ፕሮግራም እንዲካሄድባት የተመረጠችው በዋናነት የገጠሩም ሆነ የከተማው ነዋሪ መገናኛ ማዕከል ሆነ ስለምታገለግል ነው፡፡ ከተማዋ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት ብታስመዘግብም በርካታ የከተማዋና የአካባቢዋ ነዋሪዎች ላይ የፋይናንስ ዕውቀት ውስንነት፣ የፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽነት ላይ እንቅፋቶች እና በቂ የሆነ የፋይናንስ መረጃ አለማግኘት ይስተዋላል፡፡

የገጠሩን ማህበረሰብ የፋይናንስ ዕውቀት ማጎልበት የብሔራዊው ፋይናንስ ስትራቴጂ ዋና አካል ነው፡፡ ይህም ጋምቤላ ክልልን የፋይናንስ ግንዛቤ በመፍጠር፣ አካታችነትን በማጠናከርና የገጠሩን ማሕበረሰብ በመረጃ ላይ የተመሠረት ውሳኔ እንዲወስኑ በማስቻል ረገድ ዋነኛ መነሻ ያደርጋታል፡፡

ከጥቅምት 17 – 21፣ 2018 ፡ አገር አቀፍ ዘመቻ – መክፈቻ መርሃግብር በጋምቤላ ክልል

የዘመቻው ግቦች እና ዓላማዎች

በአገር አቀፍ ደረጃ የሞባይል ገንዘብ ግንዛቤና አጠቃቀምን ማሳደግ

ግለሰቦች በተለይም ሴቶችና በአግባቡ አገልግሎት ያልተደረሰባቸው ቡድኖች አስተማማኝ የሆነ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን በአግባቡ ተገንዝበው ተጠቃሚ መሆናቸውን ማረጋገጥ

የሴቶችን የፋይናንስ ተደራሽነት ሂሳብ በማስከፈትና በሌሎች አገልግሎቶች ማስፋት

የሒሳብ ማስከፈት ዘመቻዎችን፣ የማህበረሰብ ተሳትፎዎንና የሥራ ቦታ አካታችነት ላይ ትኩረት በማድረግ የሴቶችን የፋይናንስ ተደራሽነትና ተጠቃሚነት ማሳደግ

በደንበኞች ጥበቃ ህዝቡ በፋይናንስ ተቋማት ላይ ያለውን እምነት ማጠናከር

ደንበኞች ስለመብታቸው፣ግዴታቸውና ቅሬታ አፈታት ላይ ያላቸውን ግንዛቤ በማሳደግ በፋይናንስ ሥርዓቱ ላይ ያላቸውን መተማመን መገንባት


በባለድርሻ አካላት መካከል ትብብርን ማጎልበት

የፋይናንስ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የመንግሥት አካላት፣ የልማት አጋሮችና የሲቪል ማህበረሰቡን በማስተባበር የፋይናንስ ትምህርትንና አካታችነትን ማበረታታት


ግልጸኝነትንና በመረጃ ላይ የተመሠረቱ ውሳኔዎችን ማሳድግ

በጾታ የተከፋፈለ መረጃ በመሰብሰብ፣ የዳሰሳ ጥናት በማካሄድ፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ክትትል በማድረግ አካታችነትንና ተጽእኖን መለካት

ሴቶችንና የፋይናንስ አገልግሎት በአግባቡ ያልተዳረሰባቸው ማህበረሰቦችን ማገዝ

ስለሞባይል ገንዘብ ተግባራዊ ሥልጠና መሥጠት፣ ተግባራዊ ማሳያዎችን ማካሄድ፣ በፋይናንስ ተቋማት ያሉ ሴት ሠራተኞችን ጭምር ያካተተ ፕሮግራም በማዘጋጀት የአመራር ሥልጠና መስጠት

የወጣቶችን ተሳትፎና ሥራ ፈጠራን መደገፍ

የፋይናንስ ትምህርትን ከሥራ ፈጠራና ሥልጠና ጋር በማስተሳሰር የወጣቶችን የሥራ ፈጠራ ዕድል ማጠናከር




በትምህርት ቤቶች የፋይናንስ ትምህርትን ማጠናከር

የፋይናንስ አቅምን ከታች ጀምሮ ለመገንባት የፋይናንስ ትምህርት ሞጁሎችን መደበኛና ኢመደበኛ በሆኑ የትምህርት ፕሮግራሞች ማስተዋወቅ

የፋይናንስ ዕውቀት ሳምንት ቀጣይ መዳረሻዎች

ዋናዋና ተግባራት

የፋይናንስ ደንበኞች ጥበቃ

የማህበረሰብ አቀፍ ተሳትፎ

የፋይናንስ ትምህርት ለገጠሩ ማህበረሰብ

የሴት የፋይናንስ ተቋማት ሠራተኞች ወርክሾፕ

የጎዳና ላይ ትእይንት ዘመቻ የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ላይ

ወጣቶች

በጾታ የተከፋፈለ መረጃ :
እሴትና ግቦች

Value of FLW

በጾታ የተከፋፈለ መረጃ እሴቶች

በጾታ የተከፋፈለ መረጃ ለተለያዩ ቡድኖች የፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽ እንደሆነ ምንያህል ተጠቃሚና ትርፋማ እንደሆኑ ለመረዳት አስፈላጊ ነው፡፡ እንደዚህ አይነት መረጃ ከሌለ የፋይናንስ አካታችነት እቅስቃሴዎች የተወሰኑ የህብረሰተብ ክፍሎች ያሉባቸውን ችግሮች ያለመገንዘብ ስጋት ይፈጥራል፡፡

እንደዚህ አይነት መረጃዎችን መሰብሰብና መተንተን የፋይናንስ ተቋማት፣ ፖሊሲ አውጭዎችንና የልማት አጋሮችን

FLW Check Icon

በፋይናንስ ዕውቀት፣ ምርቶች፣ ተደራሽነትና ተጠቃሚነት ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ያሉባቸውን ክፍተት ለመለየት ያስችላል

FLW Check Icon

የፋይናንስ አካታችነትን አገልግሎቱ በአግባቡ ያልተዳረሰባቸው ክፍሎችን ለማዳረስ የሚደረገውን ጥረት ለመከታተል ይረዳል

FLW Check Icon

የተለያዩ ፍላጎቶችንና ነባራዊ ሁኔታዎችን ታሳቢ ያደረጉ የፋይናንስ ምርቶችንና አገልግሎቶችን ለማቅረብ ያስችላል

FLW Check Icon

በፋይናንስ ዘርፉ ውስጥ ፍትሃዊነትን ለማስፈን የሚያስችል ተጠያቂነትንና ተደራሽነትን ያጠናክራል

FLW Check Icon

ሁሉን አቀፍ የሆነ የኢኮኖሚ ተሳትፎ ለማምጣት የመረጃ ግብዓት በማቅረብ የተመረጡ ፖሊሲዎችንና ፕሮግራሞችን ለመቅረጽ ያግዛል

በ 2018 የፋይናንስ ትምህርት ሳምንት ላይ በጾታ ላይ የተመሠረተ መረጃ አሰባሰብን በማጉላት የተሳትፎ ሂደቶችን የሚታዩ፣ የሚለኩና በድርጊት የተሞሉ መሆናቸውን እናረጋግጣለን፡፡

Value of FLW

የፋይናንስ ዕውቀት ሳምንት ምን ለማሳከት አቅዷል?

ጾታን መሠረት ያደረገ መረጃ የመሰብሰቢያ ሥርዓተን በመዘርጋት የፋይናንስ ትምህርት ሳምንት፣

FLW Check Icon

የተሳትፎ ሂደቶችን ተከታትሎ መያዝ፡ – ከተለያዩ ቡድኖች ውስጥ ማን ነው ሥልጠናዎችን እየተሳተፈ ያለው፣ ሒሳብ እየከፈተ ያለውና በሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ላይ እየተሳተፈ ያለው

FLW Check Icon

ተጽእኖዎችን መገምገም፡ ከሌሎች ጋር ሲነጻጸር በፋይናንስ ትምህርት ጣልቃ ገብነት በአግባቡ የፋይናንስ አገልግሎት ያልተዳረሰባቸው የህብረተስብ ክፍሎች ምንያህል ተጠቃሚ እንደሆኑ መረዳት

FLW Check Icon

በመረጃ ላይ የተመሠረተ ውሳኔ አሳጣጥን መደገፍ፡ – ብሔራዊ ባንክን፣የፋይናንስ ተቋማትንና የልማት አጋሮችን የተሻላ አካታች የፋይናንስ ስትራቴጂ እንዲኖራቸው ትክክለኛ አቅጣጫን ማሳየት

FLW Check Icon

ተጠያቂነትን ማበረታታት፡ ተቋማት በእኩል ደረጃ ክትትል አድርገው መረጃ ማቅረባቸውን ማረጋገጥ

FLW Check Icon

ቀጣይነትን መገንባት፡ አካታች የሆነ የፋይናንስ ትምህርትና የደንበኞች ጥበቃን የመከታተልና መረጃ ለመሰብሰብ ሂደት መሠረት ቀጣይነት ያለው መሠረት ማስቀመጥ

በመጨረሻ፣ የፋይናንስ ዕውቀት ሳምንቱ ዓላማ የተሳተፉትን ብዛት መቆጣጠር ብቻ ሳይሆን፣ የተለያዩ ቡድኖች ተሞክሮና ፍላጎቶች የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ወደፊት እንዲመራ መረጃ ማቅረብ ነው፣ በብሔራዊው የፋይናንስ ትምህርት ስትራቴጂና በተጨማሪም የፋይናንስ ሴቶች ጥምረት በNEWFin በተቀመጠው ራዕይ መሠረት የተካተተና እና እውነተኛ ፋይናንስ ሥርዓትን ማሳደግ ነው፡፡

አጋር ድርጅቶች